
About
በኪሱሙ የራይላ ኦዲንጋ መታሰቢያ ዝግጅት ላይ በርካታ ሰዎች መቁሰላቸውን የኬንያ ቀይ መስቀል ባለሥልጣናት ተናገሩ። የፈረንሳዩ ቢኤንፒ ፓሪስባስ ዩናይትድ ስቴትስ ሱዳን ላይ የጣለችውን ማዕቀብ በመተላለፍ በሰጠው የባንክ አገልግሎት የኦማር አል-በሽር መንግሥት የዘር ማጥፋት እንዲፈጽም ረድቷል በሚል በአሜሪካ ፍርድ ቤት ጥፋተኛ ተባለ። በእስራኤል እና በሐማስ ጦርነት የተገደሉ ፍልስጤማውያን ቁጥር ከ68,000 በላይ መድረሱን የጋዛ የጤና ሚኒስቴር ዛሬ ቅዳሜ አስታወቀ። ኢራን ከአስር ዓመታት በፊት በኑክሌር መርሐ-ግብሯ ላይ ከልዕለ-ኃያላኑ የተፈራረመችው ሥምምነት በማብቃቱ በውሉ በተካተቱ ገደቦች እንደማትገዛ አስታወቀች።