
About
-የእስራኤል ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ጌዲዮን ሰዓር ራስዋን የሶማሊላንድ ሪፐብሊክ ብላ የምትጠራዉን ግዛት ጎበኙ።ሶማሊያ የእስራኤሉን ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ጉብኝትን «ሕገ-ወጥና ዋጋ ቢስ» በማለት አዉግዛዋለች።--የዩናይትድ ስቴትስ ባለሥልጣናት የቬኑሱዌላዉን መሪና ባለቤታቸዉን ማገታቸዉን የቀሰቀሰዉ ተቃዉሞ እንደቀጠለ ነዉ።የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ኮሚሽነር ዛሬ እንዳለዉ የአሜሪካ ርምጃ «ጉልበተኞች የፈለጉትን ማድረግ ይችላሉ የሚል መልዕክት ያስተላልፋል።» -የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ግሪላንድን ከዴንማርክ ለመንጠቅ በድጋሚ መዛታቸዉን ሰባት የአዉሮጳ ሐገራት መሪዎች ተቃወሙት።