
About
የኢራን የፍትሕ ሚኒስትር በሐገሪቱ ሰልፍ በሚያካሂዱት ላይ በቸልታ እንዳማያልፉ አስጠነቀቁ። የቀድሞው የሩስያ ፕረዚደንት ዲሜትሪ ሜድቪዴቭ፤ «የጀርመን መራሔ መንግስት ፍሬደሪሽ ሜርስም እንደ ቬንዙዌላው ፕረዚደንት በተመሳሳይ ወታደራዊ ዘመቻ ሊታገቱ ይገባል» ሲሉ የሰጡትን አስተያየት በርሊን በጥብቅ አወገዘች። ዩናይትድ ስቴትስ እንደ ዓለም ዳኛ ሆና እየተንቀሳቀሰች ነው ሲል የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከሰሰ።