About
-የኢትዮጵያ የፈደራል መንግስት ጦር መቀሌ አጠገብ የሚገኝ ሥፍራን ዛሬ በሰዉ አልባ አዉሮፕላን ደብድቧል በማለት ህወሓት ወቀሰ።ህወሓት በድብደባዉ ሥለደረሰዉ ጉዳት አልገለፀም።አንድ የዓይን ምስክር ግን ቢያንስ አንድ ታጣቂ መገደሉንና ሌሎች ሁለት መቁሰላቸዉን አስታዉቀዋል።---የዩናይትድ ስቴትስ የፌደራል ፍርድ ቤት ለኢትዮጵያዉያን የተሰጠዉ አሜሪካ የመኖርና የመሥራት ጊዚያዊ ፈቃድ እንዲሰረዝ ወሰነ።--የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚደረግም፣ ሊደረግ የታቀደም ድርድር የለም አሉ።የኢራን ባለሥልጣናት እንደሚሉት ግን ዩናይትድ ስቴትስ የገባችዉን ግዴታ ካላከበረች ሥልታዊዉ ወሽመጥ አይከፈትም።