የሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና
22 April 2026

የሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና

የዓለም ዜና

About
በአማራ ክልል የዋግ ህምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን አበርገሌ ወረዳ፣ ከትናንት በስቲያ ሰኞ ጠዋት ጀምሮ በተቀሰቀሰ ጦርነት የአካባቢው አስተዳደር ሰራተኞች መታገታቸው እና ንጹሃን ሰዎች መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ለዶይቸ ቬለ ገለጹ። የቀድሞ የሰላም ሚኒስቴር ዴኤታ እና የኦሮሚያ ክልል ምክር ቤት (ጨፌ ኦሮሚያ) አባል የአቶ ታዬ ደንደዓ አዲሱ ክስ ተቋረጠ።የኒጀር መንግሥት  2900 የሀገር ውስጥ እና የውጭ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እንቅስቃሴን አገደ።ኢራን በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ መርከቦች ላይ መተኮሷን ቀጥላለች።ሉፍታንዛ 20,000 የአጭር ርቀት በረራዎችን እንደሚሰርዝ አስታወቀ።