
About
• የደቡብ ሱዳን ጦር እና በአማጽያን መካከል የተቀሰቀሰውን አዲስ ግጭት ሽሽት ከ100 ሺ በላይ የአኮቦ ከተማ ነዋሪዎች ድንበር አቋርጠው ኢትዮጵያ መግባታቸውን የተባበሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት ዩኒሴፍ አስታወቀ። • የሶማሊያዋ የጁባላንድ ግዛት አስተዳደር ከሞቃዲሾው ፌዴራላዊ መንግስት ጋር ያለውን ማንኛውንም ዓይነት ግንኙነት እና ትብብር ማቋረጡን አስታወቀ። • በሰሜናዊ ምስራቅ ናይጄሪያ በደረሰ ተከታታይ የአጥፍቶ መጥፋት የቦምብ ጥቃት በትንሹ 23 ሰዎች ተገደሉ። • እስራኤል ከፍተኛውን የኢራን የደህንነት ባለስልጣን አሊ ላሪጃኒን መግደሏን አስታወቀች።