የመጋቢት 2 ቀን 2018 የዓለም ዜና
11 March 2026

የመጋቢት 2 ቀን 2018 የዓለም ዜና

የዓለም ዜና

About
-ደቡብ ኢትዮጵያ ጋሞ ዞን ዉስጥ በደረሰ የመሬት መደርመስና የጎርፍ አደጋ በትንሹ 64 ሰዎች ሞቱ።ሌሎች በርካታ ሰዎች የደረሱበት አልታወቀም።---ሱዳን ዉስጥ ለቀስተኞችን አሳፍራ ትጓዝ የነበረች አነስተኛ የጭነት መኪና (ፒክ አፕ) በሰዉ አልባ አዉሮፕላን (ድሮን) ተመትታ 40 ሰዎች ተገደሉ።በሌላ የሰ,ዉ አልባ አዉሮፕላን ጥቃት 17 ሰዎች ተገድለዋል።አብዛኞቹ ሴት ተማሪዎች ናቸዉ።---እስራኤልና ዩናይትድ ስቴትስ በኢራን ላይ የከፈቱት ጦርነትና የኢራን አፀፋ የዓለምን ምጣኔ ሐብት እያዉገረገረዉ ነዉ።ጦርነቱ እንዲቆም የተለያዩ መንግስታትና የኃይማኖት መሪዎች የሚያደርጉት ጥሪና ፀሎት እንደቀጠለ ነዉ።ጦርነቱም አላባራም።