የመጋቢት 06 ቀን 2018 የዓለም ዜና
15 March 2026

የመጋቢት 06 ቀን 2018 የዓለም ዜና

የዓለም ዜና

About
የኢትዮጵያ መንግሥት የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ የመሸጫ ዋጋ ላይ ያደረገውን ጭማሪ ተከትሎ በአዲስ አበባ የሕዝብ መጓጓዣ ከ5 እስከ 20 ብር የታሪፍ ማሻሻያ ተደረገ። የሩሲያ ጦር በዩክሬን በመካሔድ ላይ ለሚገኘው ጦርነት ኬንያውያንን በግዳጅ ከመመልመል እንዲታቀብ ግፊት ለማድረግ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሙሳሊያ ሙዳቫዲ ወደ ሞስኮ አቀኑ። በኮንጎ ሪፐብሊክ ዜጎች ድምጽ ሲሰጡ ዋሉ። አሜሪካና እስራኤል ከኢራን የገጠሙትን ጦርነት የቀሰቀሱ መሪዎች ውጊያውን እንዲያስቆሙ የሮማ ካቶሊካዊት ቤተ-ክርስቲያን ርዕሰ-ሊቃነ ጳጳሳት ሊዎ 14ኛ ጥሪ አቀረቡ። ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በባርሴሎና እና በሴዑል የተካሔዱ የማራቶን የሩጫ ውድድሮችን አሸነፉ።