
About
-ሱዳንን ከኢትዮጵያ ጋር በሚያዋስነዉ የሴቲት ወንዝ ዉስጥ 15 የትግራይ ተዋጊዎች አስከሬን መገኘቱን የሱዳን የሕክምና ባለሙያዎች አስታወቁ።የኢትዮጵያ መንግሥት ጦርና የህወሓት ተዋጊዎች አዲስ የገጠሙት ዉጊያና የዉጊያ ዝግጅት ሰላማዊ ሰዎችን ለከፋ አደጋ እንደሚያጋልጥ አምንስቲ ኢንተርናሽናል አስጠነቀቀ።-ዩናይትድ ስቴትስና ኢራን የሚያደርጉት ድርድር አግባቢ ዉጤት እያሳየ መሆኑን አደራዳሪዎችና የአሜሪካ ባለሥልጣናት አስታወቁ።-የእስራኤል ጦር የዛሬ ሶስት ዓመት ግድም ጋዛ ከተማ ዉስጥ በጅምላ የገደላቸዉ 112 ፍልስጤማዉያን ዛሬ በጅምላ ተቀበሩ።