About
አርስተ ዜና፤ በጫካ የሚገኙትና የፋኖ ንቅናቄ ተራ አባል ነኝ ሲሉ የገለፁልን አቶ እስክንድር ነጋ፤ ባለፉት አራት ዓመታት ከበርካታ የግድያ ሙከራ ማምለጣቸዉን ተናገሩ። እስክንድር ነጋ ጽምዶ የተባለዉን ጥምረት ን የኢትዮጵያ ጠላት ብለዉታል።-ዛሬ 35 ኛ ዓመት የነጻነት ቀንዋን ዛሬ ያከበረች ዩክሬይን መዲናዋ ላይ አዲሱ የዩናይትድ ኪንግደም ጠቅላይ ሚኒስትር አንዲ በርንሃምን ጨምሮ የአዉሮጳ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ተገኝተዋል።- በመካከለኛው ምስራቅ የቀጠለዉን ግጭት ተከትሎ የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራጋቺ፤ የአሜሪካን ከኢራን ጋር ስላለው ግጭት መፍትሄ ለማግኘት ከቴህራን ጋር በአክብሮት መነጋገር እንዳለባት አጽኖት ሰጡ።