Skip to content
Opens in a new window
DW Amharic የነሐሴ 10 ቀን 2018 የዓለም ዜና
16 August 2026

DW Amharic የነሐሴ 10 ቀን 2018 የዓለም ዜና

የዓለም ዜና

About
የኢትዮጵያ ፌድራል መንግሥትና የትግራይ ክልል “የፖለቲካ መሪዎች የሕዝቡን ድምጽ እንዲሰሙ፣ ሰዎችን እየጎዱ ያሉ ችግሮችን የጋራ መግባባት በመፍጠር ለመፍታት እንዲሞክሩ” የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጥሪ አቀረበ። የሱዳን የሽግግር ሉዓላዊ ምክር ቤት ሊቀ-መንበር አብደል ፋታኅ አል-ቡርኻን በሱዳን ሊካሔድ ለታቀደው ብሔራዊ ውይይት ተሳታፊዎች “ሕጋዊ፣ ፖለቲካዊና የጸጥታ ዋስትና” ለመስጠት ቃል ገቡ። ለሊቱን በሩሲያና በዩክሬን በተፈጸሙ ኃይለኛ የድሮንና የሚሳይል ጥቃቶች በሁለቱም ሀገራት 12 ሰዎች መገደላቸውን ባለሥልጣናት አስታወቁ።