About
የኢትዮጵያ ፌድራል መንግሥትና የትግራይ ክልል “የፖለቲካ መሪዎች የሕዝቡን ድምጽ እንዲሰሙ፣ ሰዎችን እየጎዱ ያሉ ችግሮችን የጋራ መግባባት በመፍጠር ለመፍታት እንዲሞክሩ” የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጥሪ አቀረበ። የሱዳን የሽግግር ሉዓላዊ ምክር ቤት ሊቀ-መንበር አብደል ፋታኅ አል-ቡርኻን በሱዳን ሊካሔድ ለታቀደው ብሔራዊ ውይይት ተሳታፊዎች “ሕጋዊ፣ ፖለቲካዊና የጸጥታ ዋስትና” ለመስጠት ቃል ገቡ። ለሊቱን በሩሲያና በዩክሬን በተፈጸሙ ኃይለኛ የድሮንና የሚሳይል ጥቃቶች በሁለቱም ሀገራት 12 ሰዎች መገደላቸውን ባለሥልጣናት አስታወቁ።