
About
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ በጥሞና ወቅት “ፕሮጀክት ማስጀመር እና ማስመረቅ” ከለከለ። ክልከላው የምርጫውን ተዓማኒነት ለማረጋገጥ ያግዛል በተባለው የጥሞና ጊዜ ከማይደረጉ እንቅስቃሴዎች ውስጥ የተካተተ ነው። ከኢትዮጵያ መንግሥት የሚዋጋው የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ከነገ ጀምሮ በአማራ ክልል “ለተከታታይ አምስት ቀናት ከአንቡላንሶች በስተቀር ሁሉም መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ መደረጋቸውን” አስታወቀ። የኢትዮጵያ መንግሥት አገሪቱ አንድ ቢሊዮን ዶላር የተበደረችበት ቦንድ ባለቤቶችን ከሚወክል ጊዜያዊ ኮሚቴ ጋር ያደረገው ውይይት ውጤታማ ሳይሆን መቅረቱን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ።