
About
ባለፉት ጥቂት አመታት የዩናይትድ ስቴትስና የእስራኤል መሪዎች በወሰዱት እርምጃ የዓለም የዲፕሎማሲ ማዕከልነቱ የተሽመደመደዉ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዲፕሎማቶችም የዋሽግተንና የቴሕራን መሪዎች ጦርነት ከመግጠም እንዲታቀቡ አደራ ብለዋል።በለንደን ስኩል ኦፍ ኤኮኖሚክስ የዓለም አቀፍ ግንኙነት ፕሮፌሰር ፋዉዝ ጀርጀስ እንደሚሉት የዲፖሎማሲ ጥረት እየከሰመ፣ የጦርነቱ አይቀሬነት እየደመቀ ነዉ።