
About
የምዕራብ አዉሮጳ መንግሥታት የእስራኤን አለመቃወማቸዉን ሲያስታዉቁ፣ ትራምፕ እስራኤልን ደግፈዉ ኢራንን ደበደቡ።ኢራንን የኑክሌር ተቋማት ሙሉ በሙሉ አወደምን አሉም።12 ቀናት ያስቆጠረዉ የእስራኤል-ዩናይትድ ስቴትስና የኢራን ጦርነት በተለይ ኢራንና እስራኤል ዉስጥ የሰዉ ሕይወት ከማጥፋቱ በተጨማሪ ከፍተኛ የምጣኔ ሐብት ኪሳራ አስከትሏል።ዩናይትድ ስቴትስም ለ18 ሰዓታት ድብደባ ወደ 2 ቢሊዮን ዶላር አዉጥታለች።የ12ቀናቱ ድብደባማ ሆነ ትራምፕ ያወ,ጁት ድል የእስራኤል፣ የዩናይትድ ስቴትስና የኢራን መሪዎች ለተጨማሪ ጦርነት ከመዛዛት፣ በጦር ኃይል ከመፋጠጥ አለማዳኑ እንጂ እንቆቅልሹ።ፍጥጫዉ ዛሬም እንደቀጠለ ነዉ።