zeno
Create a Station
Explore
Religious
Music
News
Podcasts
Bible
By Genre
By Location
By Language
Download App
Toggle Sidebar
zeno
DW | Amharic - News
Amharic
News, Analysis and Service from Germany and Europe - in 30 Languages
Website
Episodes
13
16 March 2026
ማሕደረ ዜና ፣ የእስራኤል-ዩናይትድ ስቴትስና የኢራን የዉጊያ ሥልትና መልስ የለሽ ጥያቄዎች
አላማን በአነስተኛ ኪሳራ ከግብ ለማድረስ የተዋጣለት፣ብዙ ገንዘብ የፈሰሰበት፣አጀማመሩ ለእስራኤል-አሜሪካኖች ጥሩ ነበር።ግን አልተሳካም-ይላሉ ሥልት አዋቂዎች።ምክንያቱ ብዙ ነዉ።ዋናዎቹ ግን ሶስት።ቀዳሚዉ የቱርኩ ፕሬዝደት ሬሴብ ጠይብ ኤርዶኻን ባለፈዉ ሳምንት እንዳሉት አጠቃላይ ጦርነቱ በተንጋደደ ስሌትና ጥንቃቄ ባልተደረገበት ዉሳኔ መጀመሩ ነዉ።
16 March 2026
በሰሜን ወሎ ዞን ሙጃ ወረዳ መንገዶች መዘጋታቸው ያስከተለው ማኅበራዊ ቀውስ
በሰሜን ወሎ ዞን ሙጃ ወረዳ በፋኖ ታጣቂዎችና በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች መካከል እየተካሄደ ባለው ጦርነት ሳቢያ የትራንስፖርት አገልግሎት ሙሉ በሙሉ በመቋረጡ፣ ነፍሰ ጡር እናቶችና ህሙማን ለከፍተኛ ስቃይና ሞት እየተዳረጉ መሆኑ ተገለጸ።
16 March 2026
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ነዳጅን በቁጠባ ስለመጠቀም የሰጡት ማሳሰቢያ
ለነዳጅ አከፋፋዮች ማደያዎችና ተጠቃሚዎች መልእክት ያስተላለፉት ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ ነዳጅን በቁጠባ ለመሠረታዊ ነገሮች ቅድሚያ በመስጠት በሃላፊነት ስሜት እንድንጠቀም ሲሉም አሳስበዋል።የነዳጅ ዋጋ ከዚህም ከናረ የውጭ ምንዛሪያችን ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ ያመጣል ያሉት የመስኩ ባለሞያ ጫናው በኢኮኖሚው ላይ የሚሳድረው ተጽእኖ ጉልህ ሊሆን ይችላል ብለዋል
16 March 2026
የጀርመን የምርጫ ሥርዓት እና ጠቃሚ ልምዶች
የጀርመን የምርጫ ሥርዓት ኢትዮጵያን ጨምሮ ፌዴራላዊ የመንግሥት አወቃቀር ከሚከተሉ ብዙ ሀገራት ይለያል። በሀገሪቱ ከጎርጎሪያኑ 1957 ወዲህ የተቋቋሙ መንግሥታት ተጣማሪ መሆናቸው አንዱ ልዩ የሚያደርገው ነው።የሀገሪቱ የፌዴራል ሥርዓት አካል የሆኑት 16 ክልሎች የፌዴራሉ የምርጫ አስፈፃሚ ተቋም ጣልቃ የማይገባበት የየራሳቸው የምርጫ ተቋም አላቸው።
16 March 2026
በሆርሙዝ ወሽመጥ ለመርከቦች እንቅስቃሴ ደኅንነት ትራምፕ ለአጋሮቻቸው ያቀረቡት ጥሪ እና አውሮጳ
እሥራኤልና ዩናይትድ ስቴትስ በኢራን ላይ የከፈቱት ጦርነትና የኢራን የአጸፋ ጥቃት በዓለም ዙሪያ የነዳጅ ዋጋን አንሯል። የንግድ መርከቦችን ጉዞ በሚያሳልጠው nሆርሙዝ ሰርጥ የሚያልፉ መርከቦች ላይ ጥቃት እንደምትሰነዝር በመዛቷ በዚያ ይተላለፉ የነበሩ ነዳጅም ሆነ ሌሎች ምርቶችን የጫኑ በርካታ መርከቦች እንቅስቃሴ ተሽመድምዷል።
16 March 2026
የመጋቢት 7 ቀን 2018 ዓ/ም የስፖርት ዝግጅት
በአትሌቲክስ ኢትዮጵያዉያን አትሌቶች በሳምንቱ የመጨረሻ ቀናት በተለያየ የዓለም ክፍል ታላላቅ ድሎች የተጎናጸፉባቸው ዉጤቶች ተመዝግበዋል። የኢትዮጵያ ታሌቲክስ ብሄራዊ ቡድን ፖላንድ በምታስተናግደው የዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ውድድር ላይ የመሳተፉ ነገር ገና ርግጥ አልሆነም።
15 March 2026
እንወያይ፤ የጦርነቱ ዳፋ ወደኛ እንዳይደፋ
ከኢኮኖሚ አንጻር የሖርሙዝ ሠርጥ በዓለም ገበያ ከሚሸጠው የአፈር ማዳበሪያ እስከ 30 በመቶ ወይም 16 ሚሊዮን ቶን የሚጓጓዝበት እንደሆነ ይታወቃል። የአለማችን 20 % የነዳጅ ግብይትም በዚሁ መስመር ይተላለፋል።
10 March 2026
በደቡብ ወሎ በአትሮኖስ ማርያም ገዳም በደረሰ የከባድ መሣሪያ ጥቃት ሰዎች ተገደሉ፣ ቆሰሉም
ጥቃቱም የተፈፀመው ቅዳሜ የካቲት 28/2018 ዓ/ም ከረፋዱ 3፡30 ላይ ሲሆን የቅዳሴ አገልግሎትጨርሰው ለደጀ ሰላም በተሰባሰቡ ካህናትና የአካባቢው ማህበረሰብ ላይጉዳት የደረሰ መሆኑን ነው የአይን እማኞች የሚናገሩት፡፡
09 March 2026
እንወያይ፤ የነጻ ፕሬስ እና የጋዜጠኞች ፈቃድ መሰረዝ ተጽኖ በኢትዮጵያ
ኢትዮጵያ ሰባተኛዉን አገራዊ ምርጫ ለማካሄድ ሽር ጉድ እያለች ባለችበት በአሁኑ ወቅትም ይሁን አስቀድሞ ጥቂት የማይባሉ የመገናኛ ብዙኃን ባለሞያዎች እና ጋዜጠኞች እንዲሁም በአመዛኙ "ነጻ" የሚባሉ ብዙኃን መገናኛ ዐውታሮች ፈቃዳቸው እየተሰረዘ፣ ጋዜጠኞቻቸውም የሥራ ፈቃዳቸዉን እየተነጠቁ ነዉ።
04 March 2026
በአማራ ክልል የሚካሄደው ውጊያ ወጣቶች ላይ ያስከተለው ተጽዕኖ
በአማራ ክልል በመንግሥትና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል እየተካሄደ በሚገኘዉ ጦርነት ወጣቶች ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ጉዳት አድርሶብናል አሉ። በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች የሚኖሩ ወጣቶች ጦርነቱ ባለፉት ሁለት ዓመታት እንደ ልብ ተንቀሳቅሰን እንዳንሠራ አግዶናል፤ በተለይም መፈራራትና ጥርጣሬ እንዲያድርብን አድርጎናልም ብለዋል።